የአማርኛዉ ዓለም አቀፍ መንፈሳዊ አገልግሎት
AMHARIC INTERNATIONAL MINISTRIES AND SERVICES (AIMS)
ራዕይ- ሰዎች ሁሉ በህይወታቸዉ ላይ የኢየሱስ ክርስቶስን ማዳንና ጌትነት እንዲቀበሉ ነው።
ዕሴቶች- ለቃሉ ሙላት(2ኛ ጢሞ 3፤16-17) ፤ለመንፈስ ምሪት,(ዘካ 4፤7,)፤ለአንድነት ጽናት (መዝ 133፤1-3 ) ፤ለባህል ጨዋነት,(ኤፊ 4፤17)፤ለአገልግሎት ትጋት(ቆላ 2፤6)፤ለሰባዊ ድርጊት,(ሉቃ 10፤25) ፤ለመንግስቱ ስፋት (ሐሥ 13፤3) ትኩረትመስጠት ።
ዓላማ- በእግዚአብሔር መልክ የተፈጠረውን ሕዝብ ማገልገል ሲሆን ለዚሁም ይረዳ ዘንድ የወንጌል ስርጭቶችን፣ የመነቃቅያ ሥልጠናዎች፤ሠርቶ- ማሳያ ዝግጅቶችና ሰባዊ ድጋፎችን በሀገር፤አህጉርና ዓለም አቀፍ ደረጃ ማካሄድ።
ስልቶች- የመንግሥተ ሰማያትን አመለካከት የሚያስፋፋ ማንኛውንም ስትራቴጅ እና ቴክኒክ ከግምት በማስገባት በዘመኑ ቴክኒዋሎጅ ተጠቅሞ ሰዎችን ወደ አጥናፋዊ ቤተ ክርስቲያን ለማስገባት መትጋት።
ግቦች- በዋሽንግተን ዲሲ አካባቢና በመላው ዓለም አማርኛ ቋንቋ የሚረዱና የአበሻው ትውልድ እግዚአብሔር ለምድራችን በገባው የተስፋ ቃል መሰረት እጁን ወደ አምላኩ በመዘርጋት ተባርኮ ለበረከት እንዲሆን ነው።